ታሪክ የወረሰ ትውልድ፣ ያልተወለዱ ህልሞችና የማዋለጃው መንገድ (አንዷለም አራጌ) –

የዛሬ 150 ዓመት በሕይወት ብንኖር ኑሮ ብዙዎቻችን ምንአልባት ሁላችንም በዘመኑ ከኖሩት አባቶቻችን ጋር በአንድ የአስተሳሰብና የኑሮ ዘይቤ ምህዋር ላይ እንደምንተም እገምታለሁ፡፡ የነበረውን የህይወት ከባቢ እንደዘላለማዊና የማይቀየር እውነት በመቁጠር እንደምንመላለስ አስባለሁ፡፡ ፈጣሪ በማይቋረጠው የዘመናት ጐዳና ላይ በየዘመኑ የሚያስነሳቸው ታላላቆች ግን ጨለማ ባጠቆረው ሰማይ ላይ እንደሚበር አብሪ ኮከብ ለሁሉም እንዲታዩ ሆነው ይምዘገዘጋሉ፡፡ ኢትዮጵያ በታሪክ ደርሳናቷ ላይ የሚንቦገቦጉ፣ የዘመንን ጢሻ እየመነጠሩ ከትውልዶች ጋር የሚተሙ ኢትዮጵያውያን ጀግኖች ነበሯት፡፡ አሏት፡፡ ከእነርሱ መካከል ዛሬ ከምንዘክራቸው አፄ ቴዎድሮስ አስቀድመን የመጀመሪያው እረድፍ ላይ ማንን ልናቆም እንችላለን? እውቁ የዘመናዊ ታሪክ ፀሐፊው ሊቀ – ጠበብት ባህሩ ዘውዴ Society and State in Ethiopian History በተሰኘው መፅሃፋቸው አፄ ቴዎድሮስ የመጀመሪያው ህልመኛ (Dreamer) እንደነበሩ ፣ ዘውዱን በዘመነ መሣፍንት ከወደቀበት አዘቅት በማውጣት የኢትዮጵያን ንጉሣዊ አስተዳደር ወደቀደመ ከፍታው ለመመለስ ከፍ ያለ ሥራ እንደሰሩ ያስረዳሉ፡፡ አክለውም በሀገሪቷ ጥልቅ የኃላቀርነት ደረጃ ከፍተኛ ቁጭት ይበላቸው እንደ ነበር ይነግሩናል፡፡ ከቁጭታቸውም የተነሳ እራሳቸውን ጨምረው ሕዝቡን “የታወረ፣ የደነቆረና አህያ” በማለት ጭምር ይገልፁ ነበር፡፡ በመጨረሻም ባህሩ እንደሚነግሩን በውስጣቸው ይነድ የነበረው የለውጥ እሳት እራሳቸውንም ሳያስቀር በላቸው፡፡ ዛሬ የምንዘክራቸው ካልተማረና ደህ ህዝብ ጉያ፣ እጅግ ኃላቀርና በጐበዝ አለቆች ፍልሚያ ከተመናታለች ሀገር አብራክ ተፈጥረው ታላቅ የአንድነትና የዘመናዊነትን ሕልም አርግዘው ሳይገለገሉ የዛሬ 150 ዓመት የተሰውት የአፄ ቴዎድሮስ ዝክረ በአል ላይ በመገኘቴ የሚሰማኝ ክብር እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡

መቼም እራሱን የቻለ የዘመን አውድ ቢኖረውም አፄ ቴወድሮስ በዘመናቸው ብዙ የጭካኔ ተግባራት መፈፀማቸውን ግን አንክድም፡፡ ነገር ግን አፄ ቴወድሮስን እንዳከብራቸው ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ልጥቀስ፡፡ በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ ሙሴ አንድ ለማመን የምቸገርበትን ነገር ተናግሮአል፡፡ “እነዚን በጐች ወይንም የዋህ እስራኤልአውያን ከምታጠፉ እኔን ከህይወት መፅሃፍ ደምስሰኝ” ብሎ ነበር፡፡ ለአንድ አማኝ ከፈጣሪ የሕይወት መዝገብ መደምሰስ የመጨረሻው የመስዋትነት ጥግ ነው፡፡ አፄ ቴወድሮስም አንዲት ወይዘሮ እንዳሉት ጥልቅ የሀይማኖት ትምህርት ዕውቀት የነበራቸው ነበሩ፡፡ እናም በመጨረሻዋ ሰዓት የገዛ ህይወታቸውን ሲያጠፉ በራሳቸው ላይ የምድርን ብቻ ሳይሆን የሰማይንም በሮችና መስኮቶች እየዘጉ እንደነበር ያውቁታል፡፡ ስለዚህ የዜጐችን ሕይወት ሲያጠፉና ሲቀጥፉ ኑረው ሀገርን ጥለው አልኮበለሉም፡፡ እንደአንዳዶቹም ሞትን ለማምለጥ ሲሞክሩ ትቦ ውስጥ በሞት ሰይፍ አልተቀሉም፡፡ ይልቅስ ሀገርን ከሚያሳንስ፣ ሕዝብን ከሚያኮስስና ትውልድንም አንገት ከሚያስደፋ ታሪክ ለትውልድ ጥለው ከማለፍ ይልቅ በመለኮታዊ ችሎትም ሳይቀር ተጠርቀው ወዳሲኦል ጥልቅ መወርወርን መርጠዋል፡፡ ይህ የሀገርንና የህዝብን ክብር ያስቀደመ የመስዋዕትነት ጥግ ነው፡፡ ዛሬ የዚህ ዘመን ትውልድ ከአፄ ቴወድሮስ የወረሰውም ይሄንን ከፍ ያለ የመሰዋትነት ታሪክ ነው፡፡
ቴዎድሮስን ሳስብ የሚደንቀኝ አንድ ነገር አለ፡፡በዚያን ዘመን ኢትዮጵያን የማዘመን ጥማቸውንና የታላቅነት ርሀባቸውን ከየት ቀዱት? ምንስ እንደዚያ አንቦገቦገው? እያልኩ እየጠይቃለሁ፡፡ ባህሩ እንደሚነግሩን “ በዘመነ-መሳፍንት ተወልደውና በዘመነ መሣፍንት አድገው እንዴት የዘመነ መሣፍንት ማርከሻ ሆኑ? እላለሁ፡፡ የተሰጠኝ ዕርስ በወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ ላይ ያመዝናልና ወደዚያው ላምራ ፡፡ አንድ ፍሬ ሃሳብ ግን ላክል፡፡ የቴዎድሮስ ህልም ሙሉ በሙሉ ተወልዷል ብዬ ባለሰብም ከህልፈታቸው በኃላ ተወልዷል፡፡ ከእርሳቸው የመቅደላ ላይ ውድቀት በመማር ዮሃንስና ሚኒሊክ ታላላቅ ገድሎችን ፅፈዋል፡፡ አድዋን ሳልጠቅስ ማለፍ እንዴት ብዬ እችላለሁ? የኢትዮጵያውያን ሥነ-ልቦናም ከፍ ያለ ማማ ላይ ተሰቀሏል፡፡ ነገር ግን ሀገርን በማዘመን ፍቅር ቢጦፉም ይህ ህልማቸው መሬት የለቀቀ አይመስለኝም፡፡ ጠንካራና የተማከለ ሀገር የመገንባት ህልማቸው ግን በተወሰነ ደረጃ በአፄ ኃይለስላሴ ተወልዷል ለማለት ይቻላል፡፡

ከ1935 ዓ.ም. በኋላ በባላባታዊና ባህላዊ ባለስልጣኖች ባንድ ወገን የውጭ ሀገር ትምህርት የቀሰሙና በሀገራቸው ለከት ያጣ ድህነት ቁጭት የተቃጠሉ ወጣት ኢትዮጵያን ባለስልጣኖች በሌላ ወገን መካከል የነበረው ትንቅንቅ ከቴወድሮስ ሀገርን የማዘመን ህልም ጋር የተቆራኘ ነበር፡፡ ንጉሠ ነገስት ኃይለስላሴ ሚዛን ለመጠበቅ ሲሉ በሁለቱ ወገኖች መካከል የነበረው ፍትጊያ እንዲቀጥል ቢፈልጉም ውሎ አድሮ ግን ዳፋው ህልውናቸውን ጭምር የሚጠይቅ ሆኖዋል፡፡

ከመቶ ዓመት በኋላ የሥጋና ደም ብቻ ሳይሆን የዕምነትም ወንድም አማቾቹ ገርማሜና መንግስቱ ንዋይም ቴወድሮስ ያማጡትን ሀገርን የማዘመን ምጥ ያምጡ ዘንድ ተገደው ነበር፡፡ ቴወድሮስ በመጨረሻዋ ሰዓት ለእንግሊዞች እንዳሉት “እናንተ ያሸነፋችሁኝ በስርዓት የሚመራ ህዝብ ስላላችሁ ነው” ብለው ነበር፡፡ ቀደም ብለው ይኸንን ቁጭታቸውን የሚያስታግስ የትምህርት ሥርዓትንም ሆነ የተግባቦት መስመር መዘርጋት አልቻሉም፡፡ ይልቅስ ህዝቡ ለምን ህልሜን አያልምም? ለምንስ ምጤን አያምጥም? ሲሉ ጨከኑበት፡፡ ጭካኔያቸውም ይገባቸው ነበርና መልሰው “ፈጣሪዬ ሆይ ምነው ወሰደኸኝ ህዝቡን ብታስርፈው” ይሉ ነበር፡፡

እንደ አፄ-ተዎድሮስ የከፋ ባይሆንም እነ-ጄኔራል መንግስቱም የገጠማቸው ተመሣሣይነት ነበረው፡፡ ሕዝቡ ብዙም ህልማቸው የገባው አልነበረም፡፡ ለዚህም ነው ጄኔራል መንግስቱ ይግባኝ እንደማይጠቅ በፍርድ ቤት ባደረገው ንግግር የሚያስገርም ትንቢታዊ ንግግር የተናገረው፡፡ “ወዮ ለእናንተ፣ ወዮ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሃሳቤ የገባው ቀን ወዩ ለእናንተ” ብሎ ነበር፡፡ ጄኔራል መንግስቱ ወደ ንጉሠ ነገስቱ ይግባኝ እንደማይልና ይልቅስ እንደእርሱ ለዓላማ ሲሉ ወደተሰው ወንድሞቹ ለመሄድ እንደናፈቀ ገልፆ ከሞት ከማፈግፈግ ይልቅ ወደመት ሲቸኩል ታይቷል፡፡ ሰቅራጥስ ለእውነት ሲል ከሞት ጋር እንደተጠበቀ ጀኔራል መንግስቱም ወደ ሞት ናፈቀ፡፡

ዛሬ ድረስ አያሌዎች የመደራጀትን አስፈላጊነት አበክረው ያሳስባሉ፡፡ ገርማሜ ንዋይ ምንአልባትም የመደራጀትን አስፈላጊነት ቀድሞ በመረዳት ማህበሮችን በመፍጠር የመደረጃት ሙከራ ቢያደርግም “አሁን ድረስ የዘለቀው የመሰነጣጠቅ አባዜ በጊዜው ችግር ሆኖበታል፡፡ ቴወድሮስ ህዝብ ህልማቸውን አልረዳ ሲል በብስጭት እርምጃ ይወስዱ እንደነበረው ሁሉ እነጀነራል መንግስቱም መፈንቅሉ መንግስቱ መክሸፉን ሲረዱ በብስጭት የሥርዓቱ ጐምቱ ባለስልጣናት ላይ እርምጃ ወስደዋል፤ ያልተገባ ቢሆንም፡፡
ቴዎድሮስ በፀጋዬ ገብረ መድህን ተወኔት “እውነት ትውልድ ይፋረደኝ” እያለ እንደቃተተው ሁሉ እነጀኔራል መንግስቱም የተስፋ አይኖቻቸውን በለጋ ተማሪዎች ላይ ያሳረፉ ይመስላሉ፡፡ ከመንፈቅለ መንግስቱ ሙከራ በፊት በ1951 ዓ.ም. የኮሌጅ ቀን ሲከበር የሕዝብን ብሶት ማንሳት የጀመሩት ተማሪዎች የእነርሱን ዓላማ አንግበው እንደሚንቀሳቀሱ በልባቸው የማይናወፅ እምነት ያሳደሩ ይመስላል፡፡ የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች በኢትዮጵያ በሕግ የተገደበ (Constitutional Monarch) ለማቋሟም ብሎም ልማትን ለማፋጠን በይፋ ከመናገራቸውም በላይ ከተማሪዎች ጋር ትግላቸውን የማስተሳሰር ሙከራም አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ተማሪዎች ትግል ሲቀጣጠል ከእነጀነራል መንግስቱ መገደል በኋላ ብዙ ዓመታትን አልጠየቀም፡፡ የኮሌጅ ቀንን በማክበር የተጀመረው የተማሪዎች ተቃውሞ እየተቀጣጠለ መጣ፡፡ አፄ-ኃይለ ስላሴ በትምህርት የለውጥ መሣሪያነት በማመን ከየአካባቢው ለጋ ኢትዮጵያውያንን ወደ ትምህርት ማዕድ ሲሰበስቡ አንዳንዶች” ይኸንን የደሃ ልጅ አስተምረህ አስተምረህ በራስህ ላይ መዘዝ እንዳታመጣ” ብለዋቸው ነበር፡፡ ትንቢቱ ሰመረ፡፡ የተማሪዎቹ ትግል በንጉሡ ላይ አነጣጠረ፡፡ ለንጉሱ የኮሌጅ ቀን የውርደትና የዘለፉ ቀን ሆኖ ይታያቸው ገባ ፡፡

ይኸ ሁሉ ሲሆን ግን የተማሪወቹ ጥያቄ የዴሞክራሲ ጥያቄ የሚያሰኝ መልክ አልነበረውም፡፡ ምን አልባት የዴሞክራሲን ጉዳይ በሚመለከት ከሁለት ዓመት በኋላ አዲስ አለማየሁ ለንጉሠ ነገስቱ የፃፉት ደብዳቤ የመጀመሪያዋ የፖሊቲካና የዴሞክራሲ ሰነድ ተደርጋ ልትቆጠር ትችል ይሆናል፡፡ ይልቅስ በወቅቱ የዓለማችንን ሰማይ እያመሰቃቀለ የነበረው የሶሻሊዝም አውሎ ነፋስ በኢትዮጵያ ለዘመናት የተንሰራፋው የአገዛዝ ጥቅጥቅ ደመና ላይ ይነፍስበት ገባ፡፡ ተማሪዎቹ በሀገራቸው ሥር የሰደደ ድህነትና የአፈና ስርዓት በአንድ ወገን፣ ዓለምን እያካለለ ባለው የሶሻሊዝም ርዮተ ዓለም በሌላ ወገን መናጥ ጀመሩ፡፡ የተቃውሞ ጡጫቸው በንጉሡ ላይ ብቻ ሳየሆን በኢትዮጵያ ታሪክ ላይም አነጣጠረ፡፡

አፄ ቴወድሮስም ሆኑ እነገርማሜ ያለውን ታሪክ አክብረው ሲነሱ ተማሪዎቹ ግን ለኢትዮጵያ ታሪክ ክብር አጡ፡፡ ቢያንስ ኦሮሞዎች፣ አጋዎችና፣ ትግሬዎች ያልተሣተፉበትን ታሪክ ለማስታወስ ያስቸግራል፡፡ ተማሪዎቹ ግን የኢትዮጵያ ታሪክ የፊውዳልና የአማራ ታሪክ ብቻ አድርገው ገነዙት፡፡ አሁን ድረስ የሀገራችንን መሠረት እያናጋ ያለው ዘረኝነት የትውልድ ክር የሚመዘዘውም ከተማሪዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ምንም እንኳን የስልጣን ማማ ላፍ ለመውጣት ሲባል እና ልዩነትን ለመፍታት የሀይል ፍጥጫ ለዘመናት በኋላም የላንጋኖ እንደሁነኛ መሣሪያ ተቆጥሮ ጥቅም ላይ ቢውልም በሥነ-ፅሁፍ አማካኝነት መዘላለፍ ግን ምን አልባትም በተማሪዎች የተቃውሞ ትግል ውስጥ ሳይወለድ አልቀረም፡፡ በተለይም አንዳንዶች እንደሚሉት በብሔረሰቦች ጉዳይ ላይ የተፃፈው የጥላሁን ታከለ ፅሁፍ ተጠቃሽ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ ረገድ በመዘላለፍ የተጀመረው የተማሪዎች ትግል በመገዳደል ተደመደመ፡፡

“ከእኛ ጋር ካልሆንክ ከእነርሱ ጋር ነህ” ብሎ ሌላውን ማጥቃትና መዝለፍ፣ ተመሣሣይ ዓላማና ፕሮግራም ይዞም ለስልጣን ሲባል በውሃ ቀጠነ እርስ በእርሱ መባላት የተለመደ የፖለቲካችን አካል ሆኖዋል፡፡ የተማሪውን እንቅስቃሴ ስንቃኝ በጣም ብዙ ህፀፆችን በትችት ወረጦ መርጠን መልቀም ብንችልም ለዓመኑበት ነገር ሁለንተናን አሳልፎ የመስጠት ደረጃቸው ከድክመቶቻቸው በተጓዳኝ ጐልቶ የሚቆም ትልቅ የመስዋዕትነት ማማ ሆኖ ይታያል፡፡ በለጋ እድሜያቸው ለአመኑበትና እውነት ብለው ሞትን እስከመናቅ ያሳዩት ቁርጠኝነት በጣም ያስደምመኛል፡

የፖለቲካ ባህላችን የቀረጹ የተለያዩ ነገሮችን ማንሣት ቢቻልም ይኸንን በመሠለ አጭር ፅሑፍ ላይ መነካካት ግን አደጋው ከጥቅሙ ያመዝናል፡፡ ነገር ግን ጥቅል የሆነውን የፖለቲካችን ንጣፍ ላይ ጥቂት ነገር ማለት ተገቢ ይመስለኛል፡፡ በአጠቃላይ ዘመናችን ድረስ የዘለቀው የህዝብና የገዥወች ግብግብ መሠረት አንድ ጉዳይ ላይ ይመረኮዛል፡፡ ህዝብ ሊኖረው የሚሻው የአስተደደር አይነት ገዥዎች ሊጭኑበት ከሚፈልጉት የአገዛዝ ቀንበር ጋር መጣጣም አልቻለም፡፡ ይህ በገዥዎችና በተገዥዎች መኮከል ያለውን ልዩነት ያሰመረና የተቀውምና የድጋፍ መሠረትም ሆኖ የቀጠለ ጉዳይ ነው፡፡ ገዥዎችም ህዝብም አንዱ በሌላው መገልገል ይፈልጋሉ፡፡፡ አንዱ በሌላው ላይ የሉዓላዊ ስልጠን ባለቤትነቱን፣ የሀገሩና የህልውና ባለቤት መሆኑን ማስረገጥ ይሻል፡፡ እስካሁን የዘለቀው የፖለቲካችን ችግር መሠረቱ በዋናነት ይኸው ነው፡፡ የህዝብ ሉዓላዊነት ሳይወለድ ዘመን ጠገቡ የአገዛዝ ልዕልና ቀንሷል፡፡

ፖለቲካ የተለያዩ የሕዝብ ጥቅሞችና ፍላጐቶች ታርቀውና ተቻችለው እንዲሄዱ ሁነኛ መሣሪያ ቢሆንም ተግባር ላይ ማዋል አልተቻለም፡፡ ፖለቲካ የመወጋገዣና የተቀርኖ መፈልፈያና የጥላቻ ግንብ መሰረት ከመሆን እንዲዘል አልፈቅድንለትም፡፡
ለዚህም ይመስላል በአገዛዞችና በህዝብ መካከል ፍርሃትና አለመተማመን የነገሠው፡፡ ፖለቲካችን ህዝቡ መብቱን እንዲጠይቅ የሚያበረታታ ሳይሆን ወገቡን ሰብሮ ለገዥዎች ዙፋን ይሆን ዘንድ የሚገፋፋ ነው፡፡ ገዥዎች እንዲገዝፉ ህዝብ ለእነርሱ እንዲነጠፍና እንዲኮስስ የሚያደርግ ግንኙነት ነው፤ ከጥንት እስከ አሁን፡፡ ለዚህም ነው በአምናችን፣ በዘንድሮአችንና በከርሞአችን መካከል ብዙም ልዩነት የማናየው፡፡

ምን አልባት የከፋ የከፋውን ብቻ እያየን ከበጐ ነገራችን ጋር እንዳንተላለፍ መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡ የእይታ መነፅራችንን የኢትዮጵያ አገዛዞች ከህዝብ ጋር የነበራቸውን የግንኙነት መስመር በህገ-መንግስት መሠረት ላይ ለመዘርጋት ተደጋጋሚ ሙከራዎች አድርገዋል፡፡ ወደዚያው እናዙር፡፡ ይህ ተግባር እንደበጐ ሙከራ ቢወሰድ ክፉት የለውም፡፡ በቀደመው የታሪካችን ክፍል ከ13ኛው እስከ 20ኛ ክፍለ ዘመን ክብረ-ነገስትና ፍትሀ-ነገስት በሚሉ ሁለት ድርሳናት ላይ ተመስርተው ህግና ሥርዓትን ለማስፈን ሙከራ ያደረጉ ነበር፡፡ በኋላ ላይ ግን በተለይም በአፄ ኃይለ ስላሴ ዘመን በዘመኑ ከነበረው የጃፖን ህገ-መንግስት እንደተቀዳ የሚነገርለት ህገ-መንግስት በ1923 ዓ.ም. መውጣቱን እናያለን፡፡ ይህ ህገ መንግስት ሀገሩንም ህዝቡንም ጠቅሎ ለንጉሡ የሚያስረክብ ሲሆን ለህዝብ ያጐናፀፈው መብት ዜግነትን ብቻ ይመስላል፡፡ በ1947 የወጣው ህገ-መንግስትም ቢሆንY የስልጣን ምንጩ ሕዝብ ሳይሆን መለኮት መሆኑን ያስቀጠለ ቢሆንም ተግባር ላይ በሚገባ አልዋለም እንጂ የተለያዩ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶችን የተካተቱበት ነበር፡፡

ብዙዎች በቁጭት የሚያነሱት በአገዛዙ ላይ የተቃውሞው አንቅስቃሴ ተፋፍም በቀጠለበት ወቅት በሀምሌ 30/1966ዓ.ም ተረቆ የበረው ህገ-መንግስት ጥቅም ላይ ቢውል ኖሮ ምን አልባትም ከዚያ ዘመን እስከአሁን ከምንዳክርበት የፖለቲካ፤ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ችግር አረንቋ ሊያወጣን የሚችል ወይንም እንዳንዘፈቅ የሚያደርግ መሣሪያ ይሆን ነበር፡፡ ይሁን እንጁ ተፋፍሞ የነበረው የአቢዮት እሳት የረቂቅ ህገ-መንግስቱን ህልውና ብቻ ሳይሆን የገዥዎችንም ህልውና አከሰመው፡፡ የህልመኞቻችን የሊበራል ዲሞክራሲ ህልም በህልምነት ቀረ፡፡

የደርግ ህገ-መንግስትም የስልጣን መሠረት እግዚዓብሔር ሳይሆን ሰፊው ህዝብ ነው አለ፡፡ አክሎም በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 3 ንዑስ አንቀስ 1 በኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ስልጣን ከህዝብም የሰርቶ አደሩ ነው ሲል ደነገገ፡፡ በሰራተኛው ስም ደርግ የአፈ ሙዝን ልዕልና ከፍ አድርጐ አውለበለበ፡፡ የአሁኑ የኢህአዴግ አገዛዝ ደግሞ የስልጣን ምንጭ እግዚአብሐር ወይንም ህዝብ ነው አላለም፡፡ ካስማውን ጐሣ ላይ ተከለ፡፡ የሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነት የተሰጠው ለህዝብ ሳይሆን ለየብሄሩ በየግል የሚታደል ሆነ፡፡ ኢህአዴግ ደጋግሞ ሊነግረን እንደሞከረው ህዝብ የመከረበትና ያፀደቀው ህገ-መንግስት አይደለም፡፡ የሕገ መንግስቱ አርቃቂ ኮሚሽን ሊቀመንበር የነበሩት ዶ/ር ነጋሦ እንደሚሉን ውይይቱ የተደረገው በኢህአዴግና በአንዳንድ ገለሠቦች መካከል ነበር፡፡ ያም ሆኖ እንኳን አጠቃላይ የህገ-መንግስቱ ረቂቅ ለህዝብ ቀርቦ ውሳኔ ህዝብ አልተሰጠበትም፡፡ የህዝብ የሉዓላዊነት የስልጣን ባለቤትነት ሳይሆን የገዥዎች ልዕልና ቀጠለ፡፡

ቃልና ተግባሩ ተጣጥመው ባያውቁም በኢህአዴግ ሕገ መንግስት አያሌ የመብት ድንጋጌዎች ተቀምጠዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንደሌሎቹ ህገ-መንግስቶች ሁሉ ዜጐችን ይቅርና ህገ-መንግስቱ እራሱንም ከዘመኑ አንጋቾች መታደግ አልቻለም፡፡ አሁንም ዜጐች ከወረቀት በዘለለ የሉዋዓላዊ ሰልጣን ባለቤት መሆን አልቻሉም፡፡ አገዛዝም የአፈና እንጂ የነፃነት ምኩራብ ሊሆን አይችልም፡፡ አልቻለም፡፡

ከ13ኛው እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ክብረ ነገስት ፤ ፍትሀ ነገስት ፤ ጉባኤ ሊቃውንት እና ህገ ስርዎ መንግስት ( የመንግስት አስተዳድር መመሪያ ) የሚባሉ ሰነዶች የሰላምም ሆነ የጦርነት መመሪያ ሆነው እንዳገለገሉ ሁሉ ህገመንግስቶችም በዋናነት የህዝብን መብት ለማክበር ሳይሆን የአገዛዞችን ህልውና ለማስቀጠል እና ለማጠናከር ጥቅም ላይ ውለዋል ፡፡ የህዝብን ጥቅምና መብቶች የሚያስከብሩ ሁኔታዎች ባለመኖራቸው ብዙውን ጊዜ ውቅረ መንግስቱ የመርጋት ችግር ታይቶበታል -ይታይበታል፡፡ ቀደም ብለን እንዳየነው አጼ ቴድሮስ ትልቅ ትኩረት ከሰጧቸው ጉዳዮች አንዱ የአረጋውያንና በየጎጡ የመቧደን አዙሪት ውስጥ የወደቀውን ሀገር በማዋሃድ የተሻለ ውቅረ መንግስት ላይ ጠንካራ ሀገርን መገንባት ነበር፡፡ ይህ ህልምም ቢሆን በሙላት አልተወለደም፡፡

አገዛዞቹ የቅርጽ እንጂ የይዞት ልዩነት አልነበራቸውም ፡፡ ህዝብ ሁልጊዜም ለአገልጋይነት እንጂ ለተገልጋይነት አይታጭም ፡፡ በዜጎች እና በአገዛዞች መካከል የግንኙነት መስመሩን ለመዘርጋት የሚዘጋጁ ሰነዶች ህዝብ ያመነባቸው የቃል ኪዳን ሰነዶች ሳይሆኑ ህዝብ እንዴት መገዛት እንዳለበት አበክረው የሚያሳዩ ናቸው ፡፡ ያ ማለት በሀገራችን ውስጥ ምንም አይነት የዲሞክራሲ ተሞክሮ ፈጽሞ የለም ማለት አይደለም፡፡ የሚገባውን ያህል ያልዘመርንለትና ለዓለም ያላስተዋወቅነው የገዳ ዲሞክራሲ እና በደቡብ በሀገራችን ክፍሎች አንዳንድ አካባቢዎች የነበሩ የህዝብ ተሳትፎ ላይ የተመሰረቱ አስተዳድራዊ መስተጋብሮች ነበሩን ፡፡ የህዝብ ፈቃድ መኖር እና አለመኖር አገዛዞች የሚያወርዱት አስተዳድራዊና ፖለቲካዊ መመሪያዎች እንዲሳኩ ወይንም እንዳይሳኩ የማድረግ አቅም አለው ፡፡ ለዚህም ነው ሀገራችን ለዘመናት ባለችበት የምትረግጠው፡፡ ህዝብ ስለችግር፣ ጥቅሞቹ፣ መብቶቹና ተስፋዎቹ መምከር በእነርሱም ላይ መወሰን ባልቻለባት ኢትዮጵያ ነገራችን ሁሉ የእንቧይ ከባብ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ የዛሬ 60 እና 70 አመት ከዚያም በቀደሙ አመታት ያነሳናቸው አጀንዳዎች ዛሬም አጀንዳዎቻችን ናቸው ፡፤ የትላንቱን ከዛሬ የዛሬውን ከነገ የምናስተሳስርበት የርዮት ድር የለንም ፡፡ አምናችንን እና ዛሬያችንን ተደባልቀዋል ፡፡ ነገአችንስ እንዴት ይሆን? ካለፈው እና ከዛሬው ባልተማርን መጠን ነጋችንን ከትናትና ከዛሪያችን ጋር መመሳሰሉ አይቀርም ፡፡

ከአላሚዎቻችን በመማር ነገአችንን የተሻለ ማድረግ ይገባል፡፡ ቀደም ብለን እንዳየነው የቴድሮስ ሀገሩን ከዘመነ መሳፍንት አዙሪት በማውጣት ጠንካራ፣ የረጋ እና የዘመነ ሀገርን የመፍጠር ህልም ነገን የተሻለ ማድረግ ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ የ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ከዚያም በኋላ ከአድማሳቸው ባሻገር ያለውን አለም ስልጣኔ ምን ላይ እንደደረሰ በአካል በመገኘት ያረጋገጡ ኢትዮጲያውያን ህልምም ኢትዮጵያን የማዘመን ህልም ነበር ፡፡ እነጀነራል መንግስቱ ንዋይ አያሌ ዘመናትን ካስቆጠረው ዘውዳዊ አገዛዝ ጋር ግብግብ የገጠሙት ነገን የተሻለ ለማድረግ ከሰነቁት ህልም ጋር የተቆራኘ ነው ፡፡ የኢትዮጲያ ተማሪዎች መሬት ላራሹ፣ የብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት ይከበርና ህዝባዊ መንግስት ይቋቋም የሚሉ መፈክሮችን አንግበው የወጡት በራሳቸው አውድ መሰረት ነገን ለህዝባቸው የተሻለ ለማድረግ ነው ፡፡

በእርግጥ ጊዜና ሁኔታ ተመቻችተውላቸው ያሰቡትን እርምጃ በዘመናቸው መራመድ ቢችሉ ምን ይፈጠር ነበር? የሚለውን መመለስ እንዳንችል ሁኔታዎች አይፈቅዱም ባልተፈጸመ ነገር ላይ ፍርድ መስጠት ተገቢ አይሆንም ፡፡
በኢትዮጵያ ዲሞክራሲን የማስፈን ህልም ካልተወለዱ ህልሞቻችን አንዱ ነው ፡፡ እነጀነራል መንግስቱ የንጉሳዊ ስርአቱን ስልጣን በመገደብ የተሻለ መንግስት ለመመስረት ቢያልሙ ቢሳካላቸው ኢትዮጵያን ዲሞክራሲያዊት ያደርጓት ነበር ወይ ? የሚለውን ጥያቄ በአውንታ ለመመለስ የሚያበቃ ማስረጃ የለንም፡፡ የሀምሌ 30/1966ቱ ሊብራል ህገ መንግስት ቢታወጅ ኢትዮጲያን የዲሞክራሲ ምድር ያደርጋት ነበር ወይ ? ከግምት ያለፈ መናገር አንችልም ፡፡ ህዝባዊ መንግስት ይቋቋም የሚለው መፈክር ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጲያን እንመስርት ማለት ነበር ? ነው ብዬ ለመቀበል እቸገራለሁ፡፡ በሶሻሊዝም እርእዮት አለም ፍቅር የተነደፉ ወጣቶች የህዝብን ሉአላዊነት የሚያረጋግጥ ዲሞክራሲያዊ መንግስት ይፈጥር ነበር ብዬ መቀበል ከፍ ያለ የዋህነት ይመስላል፡፡ ምክንያቱም ማርክሊዝም ህዝብን በሀይል ለአንድ ዓላማ ማስገዛት እንጂ የህዝብን ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት ማድረግ አይደለም ፡፡

የተማሪዎች ትግል ካፈራቸው የፖለቲካ ቡድኖች አንዱ የሆነው ህዝባዊ ሃርነት ትግራይ ( ህውሀት ) ስለዲሞክራሲ ሲባል አያሌዎች ዋጋ ከፍለዋል ቢልም በተግባር የምናስተውለው የቀድሞው የአገዛዝ ስርአት በአዲስ ትረካ (narration) ሲቀጥል ነው ፡፡ በትግሉ ወቅት ህይወታቸውን የከፈሉ የህውሀት ታጋዮች ዛሬ ጓደኞቻቸው በኢትዮጲያ ህዝብ ጫንቃ ላይ የጫኑትን የአገዛዝ ቀንበር ቢያዩ ምን ይሉ ነበር? ምን አልባት የተማሪዎች ትግል በጥቂት የደርግ ወታደሮች እንደተነጠቀ ሁሉ የህውሀት ትግልም የጥቂት አጤዎች መጠቀሚያ ከመሆን አልዘለለም፡፡

በ1983 ዓ.ም በአብዮት የመጣው አገዛዝ ሌላ አብዮት ባፈረጠመው አገዛዝ ሲተካ በእርስ በእርስ ጦርነት የተዳከመችው ኢትዮጵያ እና ህዝቧ ወዴት ያመራሉ? የሚለውን ጥያቄ ቁርጥ መልስ አልነበረውም፡፡ ብዙዎች የኢትዮጵያን እጣ በአውንታዊ ይወስናል የተባለው የሽግግር መንግስት ሁሉንም የኢትዮጵያ ጉዳይ የሚያገባቸው ወገኖች ያላካተተ ከመሆኑም በላይ የየብሄሩ ተወካዮችን በመደርደር በዲሞክራሲ ላይ የሚሰራ የአገዛዞች የሸፍጥ ጉዞ ተጀመረ፡፡ የሽግግር መንግስቱ ሁነኛ አካል ኦነግ ከሽግግር መንግስቱ ወጣ ፡፡ በመጣንበት መንገድ መርገጣችን ቀጠለ ፡፡

አገዛዙ ከአብዮታዊ ዴሞክራሲ ተነስቶ ወደ ሊብራል ዲሞክራሲ አመራለሁ ሲለን ለመሞኘት ተዘጋጅተን ጠብቀነው፡፡ ጋዜጠኞች ጋዜጣዎችን ማተም ጀመሩ፡፡ እንዲያውም አገዛዙ አውቆ በነፃነት እንዲጽፉ እያደረገ ነው እስኪባል ድረስ በጎ ጅማሪዎች ታዩ፡፡ ፓለቲከኞች የፓለቲካ ማህበሮችን ፈጠሩ፡፡ አለም አቀፍ ማህበረሰቡም በተግባራዊ ሂደት አገዛዙን ለመቀየር (Constructive engagement) በሚል ወዳጅነት ሽር ጉድ ማለቱን ተያያዘው፡፡ የአገዛዝ ወፍጮ ድምፅ ከሩቅ ድረስ ቢሰማም ቋቱ ላይ ግን ጠብ የሚል ጠፋ፡፡ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ሊቢራል ዲሞክራሲን ይወልድ ዘንድ ማርያም ማርያም ብንልም የተፈጥሮ ህገ አሸናፈ፡፡ አብዮታዊ ዲሞክራሲ እየደጋገመ እራሱን ወለደ፡፡

በሁሉም ዘንድ መነቃቃትን የፈጠረውን አብዮታዊ ዲሞክራሲ ሊብራል ዲሞክራሲን ይወልዳል በሚል ተስፋ ብዙዎች በአዋላጅነት የተሰበሰቡበትን ታሪካዊ ወቅት 1997ን ዛሬ እንደታሪክ ልነግራችሁ አልችልም፡፡ በቦታው ባትኖሩም እንኳን በያላችሁበት ማሪያም ማርያም ስትሉ ነበርና፡፡ የዴሞክራሲ የመወለድ ጭንቅ አገራችን ሰቅዞ ቢያሰቃያትም ሕይወቷን አልጠየቀም፡፡ የዲሞክራሲ ሺል ግን በትክክለኛ መንገድ ከእውነተኛ እና ትክክለኛ ዘር አልተገኘምና ብርሀን ሳያይ ተጨናገፈ ፡፡ ሳይወለድ ቀረ፡፡

ዲሞክራሲን የተራቡ ኢትዮጵያውያን ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከከተማ እስከ ውጪ ሀገር ልደቱን ሊያከብሩና ሊዘክሩት የነበረው የዲሞክራሲ ንጋት ለዘመናት በዘለቀው የአገዛዝ ባሩድ ጽልመት ለብሶ ዜጎች የነበራቸው የተስፋ ሙላት ወደ ጥልቅ ብሶትና የተስፋ እጦት ተቀየረ ፡፡ አያሌ ኢትዮጵያውያን ወደ ማጎሪያ ካንፖች ተጓዙ፤ የህይወትን እሸት ለመቃም የተዘጋጁ ወጣቶች በአገዛዙ አፈር በሉ ፡፡ የህዝብ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤት የመሆን ትግል በአገዛዙ ፈርጣማ ጡጫ ድባቅ ተመታ ፡፡ ህዝብ አምጦ የወለደው ቅንጅት ለአንድነት እና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ዋነኛ የአገዛዙ ሰለባ ሆነ ፡፡

የአገዛዙ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ባቡር የማስመሰያ ጭንብሉን አውልቆ በአፈና ሀዲዱ ላይ መትመም ቀጠለ፡፡ የኋልዮሽ ተምዘገዘገ፡፡ በዚህ የኋልዮሽ ጉዛ ፍርኃትን ሰብረው እና ሞትን ንቀው የሚውተረተሩ ኢትዮጲያውያንን ማደን፣ ታፔላ እየለጠፉ መቀመቅ ማውረድ የሚመጻደቅበት የጀግና ውሎ አደረገው ፡፡ በጨለመበት ሰአት ከአለም እንደሚሰወር መናኝ ለአመታት ከህዝብ፣ ከወገን እና ከሚያባቡ ልጆቻችን ተለይተን አመታትን ተጋፈጥን ፡፡ እድሜ ይፍታህ ተባልን፡፡ እድሜን የሚሰጥ ፈጣሪ እንጂ ሰው አይደለም፡፡ ውሳኔው አልሰመረም፡፡ የትግሉ መርዘም እና ማጠር በህዝብ የትግል ጽናት እንጂ በገዥዎች እብሪት አይወሰንም በመጨረሻም ለዛሬ ቀን በቃን፡፡

ዛሬ ጭላጭል ይታያል፡፡ አገዛዙ የመጣበት መንገድ የትም እንደማያደርሰው የተረዳ ይመስለኛል፡፡ ለጋ ወጣቶችን ለህዝባዊ ልእልና ሲሉ ያላቸውን የመጨረሻ መስዋእትነት ህይወታቸውን በክብር ገብረዋል፡፡ ችግሩ አገዛዙ ትግሉ ጋብ ሲል ወደ ጥንካሬው የተመለሰ ህዝቡም ያከበረውና የደገፈው ይመስለዋል ፡ ይህን አይነት ግንዛቤ አሁንም ይዘው የሚቀጥሉ ከሆነ የክፍለ ዘመኑን ታላቅ ስህተት ይሰራሉ ፡፡ አሁን አገዛዙ ለህዝብ ሉአላዊ የስልጣን ባለቤትነት ሊገዛ ግድ ይለዋል ፡፡

መፍትሄዎችን ሁሉ ከአገዛዙ እንስራ እንዲንቆረቆሩልን መጠበቅ ስህተት ነው፡፡ ኢትዮጵያን የምታክል ሀገር መፍትሄን ከአንድ ሰው መጠበቅም አይገባም፡፡ ሁሉም የራሱን ጽዋ ሊያነሳ ይገባዋል፡፡ ተቀዋሚዎች እያለፈ ያለውን ዘመን ሳያልፍብን ልንሰራ ይገባል፡፡ ከዘመነ-መሳፍንትም ሆነ ከተማሪዎች እንቅስቃሴ የሚጨለፈውን ያለመቻቻልና የመለያየት ፖለቲካ ልንቀብረው ይኸው ዘመን ግድ ይለናል ፡፡ እልህ መጋባት ያለብን ዲሞክራሲን እውን ለማድረግ እንጂ ለመጠፋፋት መሆን አይገባውም ፡፡

በሀገራችን ተጀምሮ የሚቋጭ ለውጥ ማምጣት አልቻልንም፡፡ ነገራችን ሁሉ ድንገቴ ( ) ታስቦ፣ ታልሞ የማይሰራና የማይዘልቅ ሆኗል፡፡ ዋነኛ ምክንያቱ ህዝብ የሀገሩ ባለቤት ባለመሆኑ፣ ህዝብ ያላመነበት እንቅስቃሴ ደግሞ ለውጤት አይበቃም ፡፡ ከአጼ ቴዎድሮስ ጀምሮ የኢትዮጵያ ገዢዎች ጠንካራ መንግስት ሊፈጥሩ ቢሞክሩም አልተሳካላቸውም፡፡ የህዝብ መንግስታት ስላልሆኑ፡፡ ጠንካራ መንግስት የሚባለው በመሳሪያ ክምችት፣ በሰራዊት ብዛትና በታንክ ጋጋታ አይደለም፡፡ የህዝብን ይሁንታ ያገኘና ስር በሰደደ ፍትሀዊ ተቋማት መሰረት ላይ የተገነባ መሆን አለበት፡፡ የአፄ ኃይለስላሴ ዘውዳዊ ስርዓት በ6 ወራት ትቢያ ሲሆን ታይቷል፡፡ በአፍሪካ እንኳን ገዝፎ ይታይ የነበረው የደርግ ሰራዊት በአይናችን ስር የዶግ አመድ ሲሆን አይተናል ፡፡ ጥንካሬውን በተተበተበ የጎሳ መረብ ላይ የመሰረተው የዚህ ዘመን አገዛዝም ቢሆን በህዝብ ሰላማዊ የአመጽ ትግል አጽሙ ሲቀር ሁሉም ታዝቧል፡፡ ይኸኛውን ልዩ የሚያደርገው የሀገራችን መሰረትም ማናጋቱ ነው፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያ የተረጋጋና የሰመረ ዘመን ይነጋ ዘንድ ህዝብ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤት ሊሆን ይገባዋል፡፡

የአገዛዞች የአፈና ናዳ ቢበዛም በባህላችን እና ታሪካችን ያሉን የውል ተዘክሮዎቻችንና መስተጋብሮቻችን ስር የሰደዱ በመሆናቸው የናዳውን ውርጅብኝ ተቋቁመን ለማለፍ ትልቅ ሀይል ሆነውናል፡፡ እስከ አሁን ያለው አንዱ የሌላውን ሀሳብ ትርጉም ያለመስጠት ወይንም የማበሻቀጥ ሂደት የትም አያደርስም፡፡ ተግዳሮቶቻችንን ተቋቁመን ተስፋዎቻችንን ለመጨበጥ በጋራ ታሪኮቻችን ላይ መሰማማት ይገባናል፡፡ በታሪካችን ሳንግባባ ሁላችን የምንወዳት ሀገር መገንባት አንችልም፡፡ አንዳችን የምንሰራውን ሌሎቻችን እያፈረስን እንቀጥላለን፡፡ ምክንያቱም የታሪክ ትንታኔዎቻችን ይለያያሉና፡፡ የታሪክ ህፀፅ የሌለበት ሀገርም ሆነ ሕዝብ የለም ልዩነቱ ከታሪክ ተምሮ መጭውን ዘመን በአስተማማኝ መሰረት ላይ መገንባቱ ነው፡፡

ዛሬ የሀገር አንድነትን ውቅረ መንግስት ለመፍጠር ትልቅ ተጋድሎ ያደረጉትን የአፄ ቴዎድሮስ 150 የሕልፈተ-ዓመት ስንዘክር ኢትዮጵያውን ጎሳቸውን እንደዮኒቨርስ ማየት በጀመሩበት ወቅት ነው፡፡

ዛሬ ጎሳን መሰረት ባደረገው የአገዛዙ ስሌት ሀገር ምድሩ ተናግቷል፡፡ ስነ ልቦናችን ተዛብቷል፡፡ አንዱ የእኔ ብሔር ሰው የሚለው ስልጣን ሲይዝ ሲደሰት ሌላው ስለነገው እርግጠኛ መሆን ይሳነዋል፡፡ የሰውን ልጆች ሁሉ ክብር የሚቀበል ዴሞክራሲያዊ መንግስት ይገባናል፡፡ ሁሉም የሚደመጥበትና ሀገሬ ብሎ የሚኮራበትን ማዕቀፍ መዘርጋት ለነገ የሚያድር ስራ አይደለም፡፡ በጋራ ርዕዮት ላይ የጋራ ሀገር ለመገንባት መቀራረብ መወያየትና መግባባት ተቀዳሚው አጀንዳችን ሊሆን ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ወገኖች ሁሉ የሚመክሩበት ጉባኤ መጠራት ይገባዋል፡፡ ለውጥ በተለይም መልካም ለውጥ በኢትዮጵያ ከኤሊም በላይ ያዘግማል፡፡ አሁን እንደቀድሞው እንቀጥል ዘንድ ዘመኑ አይደለም፡፡ የአጣዳፊ ለውጥ ዘመን ነው፡፡ አገዛዙ ሳይውል ሳያድር መድረኩን ሊያዘጋጅ ከሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ የፖለቲካ ሃይሎች ደግሞ ዘመኑን ለሚመጥን የፖለቲካ ለውጥ ሊዘጋጁ ይገባል፡፡

ሂሳብ የማወራረድ ባህልና ፍላጎት ዝቅ ብሎ ሊቀበር ይገባዋል፡፡ አብዛኛዎቹ የፓለቲካ ችግሮቻችን የሚፈቱት በፓለቲካ እንጂ በህግ አይደለም፡፡ በእርግጥ ዴሞክራሲን ለመገንባት የሕግ የበላይነት እንደንጣፍ ሆኖ ያገለግላል፡፡ ነገር ግን ሁሉን ነገር በህግ ቋጥረን ልናልፍ አንችልም፡፡ በይቅርባይነት አንዳችን ለሌለው የእዳ ስረዛ ልናደርግ ይገባል፡፡ “እርቅ ደም ያድርቅ” እንደሚባለው ለብሄራዊ እርቅ እና ወንድማማችነት ልባችንን አጥበንና ታጥለን መገኘት አለብን፡፡

ይህ የእርቅ መንገድ ህዝባዊ ልዕልና የሰፈነባት ጠንካራ ሀገር ትኖረን ዘንድ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህን የእርቅና የወንድማማችነት መንገድ በከፋ ችግሮች ውስጥ ተዘፍቀው የነበሩ ሀገሮች ሲጠቀሙበት አይተናል፡፡ ጊዜው አንዳችን በሌለው ውስጥ ያለውን በጎ አስተዋፅዖ ለማስተዋል ለራሳችን እድል የምንሰጥበት ነው፡፡ ጊዜው የዴሞክራሲ ለውጥ ያመጡ ዘንድ ጥቂት ግለሰቦችን የምንጠብቅበት ሳይሆን ሁላችንም ሌላውን ሳንጠብቅ ሃላፊነታችንን የምንወጣበት ነው፡፡ ጊዜው በቲኒኒሽ ድሎች የምንኮፈስበት ሳይሆን የሁላችንም የዘመናት ናፍቆት የሆነውን የዴሞክራሲ ንጋት እውን ለማድረግ ያለንን ሁሉ የምንሰጥበት ነው፡፡ ቀይ ባህር አጠገብ ቆመናል፡፡ የአገዛዝን ባህር ከፍለን ወደ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ መገስገስ ወይንም በቀጫጭን የልዩነት ድሮች ተተብትበን ባህሩ ውስጥ መስመጥ፡፡ እኔ የአገዛዝን ባህር በእርቅ፣ በፍቅርና በወንድማማችነት በትር ከፍዬ ሊሻገር ቆርጫለሁ፡፡ ነገር ግን ብቻዬን መሻገር አልችልም፡፡ ብቻዬንም መሻገር አልፈልግም፡፡ ወደ ተስፋችን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ለመሻገር የፀና የሰላማዊ ትግል መስመር ላይ አብረን ተስፋችን ሳንጨብጥ ወደኋላ ሳናይ ለመጓዝ አሁን እንቀሳቀስ፡፡ ዴሞክራሲን የማዋለጃው መንገድም ይኸው ነው፡፡
ፍትህ እንደ ቀትር ፀሐይ ፍቅር እንደ ሃይለኛ ጅረት ወንድማማችነትም እንደጉንጉን አበባ በኢትዮጵያ ላይ ይንገስ!

(ፍራንክፈርት፤ ግንቦት 2010 ዓ.ም)

Source: http://www.satenaw.com/amharic/archives/56608

Watch “ESAT Eneweyay May 09,2018” on YouTube ስለ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ስለ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከጋዜጠኛ ደረጀ ሀብተወልድ ጋር የተደረገ ውይይት።

Watch “ESAT Eneweyay February 23,2018” on YouTube

Ethiopia: Final Days of the Regime

By Graham Peebles

Under relentless popular pressure the Ethiopian Prime-Minister, Hailemariam Desalegn, has been forced to resign, other members of the government are expected to follow. In his resignation speech he acknowledged that, ”unrest and a political crisis have led to the loss of lives and displacement of many,” Reuters reports. ‘Loss of lives’ of innocent Ethiopians at the hands of TPLF security personnel to be clear. “I see my resignation as vital in the bid to carry out reforms that would lead to sustainable peace and democracy.”

This is a highly significant step in what may prove to be the total collapse of the ruling party. It has been brought about by the peaceful movement for democratic change that has swept across the country since late 2005. Protests began in Oromia triggered by an issue over land and political influence and spread throughout the country.

A little over a month ago, former Prime-Minister, Hailemariam Desalegn, announced that the government would release ‘some political prisoners’, in order, Al Jazeera reported, “to improve the national consensus and widen the democratic space.” Since then a relatively small number of falsely imprisoned people (some western media claim 6,000 but this is unconfirmed – nobody knows the exact number, probably hundreds, not thousands) have been released, including some high profile figures (Merera Gudina, chairman of the opposition Oromo Federalist Congress, Journalist Eskinder Nega and opposition leader Andualem Arage for example). Many of those set free are in extremely poor health due to the ill treatment and, in some cases, torture suffered in prison.

Despite these positive moves and the ex-Prime-Minister’s liberal sounding rhetoric, the methodology of the ruling party has not fundamentally changed: the TPLF dominated government continues to trample on human rights and to kill, beat and arrest innocent Ethiopians as they exercise their right to public assembly and peaceful protest.

The total number killed by regime forces since protests erupted in November 2015 is unclear: hundreds definitely (the government itself admits to 900 deaths), tens of thousands probably. A million people (Oromo/Somali groups) according to the United Nations have been displaced – due to government-engineered ethnic conflict – and are now in internal displacement camps (IDP’s) or are simply homeless. Tens of thousands have been falsely imprisoned without due process; their ‘crime’ to stand up to the ruling party, to dissent, to cry out for democracy, for freedom, for justice and an end to tyranny.

All ‘political’ prisoners, including opposition party members (British citizen Andergachew Tsige e.g.), and journalists, should, as Amnesty International rightly states, “be freed immediately and unconditionally………as they did nothing wrong and should never have been arrested in the first place.” Not only should all political prisoners be released forthwith, but the laws utilized to arrest and imprison need to be dismantled, and the judicial system — currently nothing more that an arm of the TPLF – freed from political control.

The primary weapons of suppression are the 2009 Anti-Terrorist Proclamation and The Charities and Societies Proclamation. Draconian legislation both, allowing the ruling party to detain anyone expressing political dissent in any form, to use torture and information elicited during torture to be used in evidence — all of which is illegal under the UN Convention against Torture, which the Ethiopian Government signed, and ratified in 1994.

Unstoppable Movement for Change

The release of a small number (relative to the total) of political prisoners and the resignation of the Prime Minister does not alter the approach of the government or their brutal method of governance. It is simply a cynical attempt by the TPLF to subdue the movement for change and to appease international voices demanding human rights be upheld.

Arrests and killings by TPLF security personnel continue unabated. Reports are numerous, the situation on the ground changing daily, hourly: At the end of January, soldiers from the Agazi force arrested an estimated 500 people in northern Ethiopia reports independent broadcaster, ESAT News. In Woldia (also in the north), TPLF soldiers forced “detainees [to] walk on their knees over cobblestones. They [TPLF soldiers] have also reportedly beaten residents including children and pregnant women.” These arrests follow the killing of 13 people in the town; “several others were killed in Mersa, Kobo and Sirinka.” And the BBC Amharic service relates that six people were killed at the Hamaressa IDP camp for internally displaced persons (IDP) (according to UNOCHA Hamaressa IDP camp was home to over 4,000 people internally displaced by the Oromo-Somali disputes) in Eastern Ethiopia. The victims were protesting against the appalling conditions in the camp and demanding they be allowed to go back to their villages when they were shot.

No matter how many people are killed, falsely imprisoned and beaten, the movement for lasting democratic change will not be put down. The principle target of protestors and activists is the dominant faction within the EPRDF coalition, the TPLF, or Woyane (relating to men from the Tigray region), as it is known. This small group took power in 1991 and has controlled all aspects of life in the country including the judiciary, the army, the media and the sole telecommunication supplier (enabling the regime to limit internet access and monitor usage) ever since. The issues driving the protests are broad, interconnected and fundamental; the fact that Ethiopia is a single party state in all but name; the wholesale abuse of human rights; the lack of freedoms of all kinds; the partisan distribution of employment, businesses, and aid; the regime’s dishonesty and corruption; state orchestrated violence false imprisonment and torture.

The people will no longer live under the suffocating blanket of intimidation that has stifled them for the last 27 years, and are demanding fundamental change, calling on the government to step down and for ‘fair and open’ democratic elections. Until now the regime’s response has been crude and predictable; rooted in force, shrouded in arrogance and unwilling to respond to the demands of the people, the government consistently falls back on the only strategy it knows: violence and intimidation; as the people march in unison, the regime unleashes its uniformed thugs. But whereas in the past fear kept people silent, now they are filled with the Fire of Freedom and Justice; they may well be frightened, but in spite of the threats more and more people are acting, engaging in organized acts of civil disobedience (stay-at-home protests) and taking to the streets in demonstration against the regime. Gatherings of thousands of people, innocent men and women, young and old, who refuse any longer to cower to the bully enthroned in Addis Ababa. And with every protestor the regime kills, beats and imprisons the Light of Unity glows a little brighter the resolution of the people strengthens, social cohesion grows.

The demand for change is of course not limited to Ethiopia; throughout the world large groups are coming together demanding freedom and social justice, cooperation and unity; the reactionary forces resist, but it is a global movement that, while it may be denied for a time, cannot be stopped. The TPLF is in chaos, their tyranny is coming to an end, they may cling on to power for a while yet, a few months, a year or two perhaps, but even if they remain in office their hold over the population is at an end. The Ethiopian people have a common foe, a unified cause, a shared purpose. The TPLF is the foe, the cause is their removal and the purpose is to bring lasting democratic change to Ethiopia, and no matter what the regime does, this time they will not be stopped.

Source: Counter Punch

Ethiopia army accused of deadly attack on IDP camp in Oromia

An attack on internally displaced persons (IDP) in Ethiopia’s Oromia region has claimed the lives of six people with others sustained varied degrees of injuries.

According to the Addis Gazette portal, the incident happened when federal forces opened fire on the Hamaressa IDP camp located in the East Hararghe Zone of the Oromia region. The portal adds that this is the second such attack on the camp.
It is not immediately known officially what led to the firing of live bullets by the federal forces. But a pro – government blogger Daniel Berhane said it was as a result of an attack by rampaging youth in the camp and village on a convoy with food supply destined for the camp.
He adds that an overwhelmed Oromia police then called for military reinforcement which intervention led to three deaths by his account. Photos shared on social media showed a number of casualties with wounds at a medical facility.
According recent figures from the United Nations body, OCHA, Hamaressa IDP camp was home to over 4,000 people internally displaced by the Oromo-Somali inter-communal disputes that started in 2017.
Figures from the U.N. and other relief agencies indicate that over a million people were displaced by the crisis. The figure is way above the government’s projections. Addis Ababa has said it was working to resettle the displaced population as quickly as practicable.
Last year at the height of the clashes between the Oromia and Ethiopia-Somali region which share a long common border, the government announced that federal forces had been banned from patrolling the common border as a key security measure.
Source: African news
  

Ethiopia’s Eskinder Nega refuses to sign false confession in exchange for prison release

February 9, 2018 11:58 AM ET
Eskinder Nega is still in jail after refusing to sign a false confession in exchange for freedom. (Eskinder family)

The Committee to Protect Journalists condemns the Ethiopian government’s attempts today to compel Ethiopian journalist and blogger Eskinder Nega to sign a false confession before releasing him under a presidential pardon. 

Eskinder, who has spent almost seven years in jail for his work, was one of 746 prisoners due to be pardoned by President Mulatu Teshome on February 8, according to media reports.

“Through this deplorable behavior the Ethiopian government is undermining any goodwill it might have generated by releasing an innocent man from prison,” said CPJ Africa Program Coordinator Angela Quintal. “Ethiopian authorities should immediately release Eskinder Nega without condition.”
At 11 a.m. local time, a prison official asked Eskinder to sign a form which falsely stated that he was a member of Ginbot 7, an organization that the government deems a terrorist group, Eskinder’s wife, Serkalem Fasil, told CPJ. Eskinder refused and asked to see a more senior official. That request was not granted and the journalist was returned to his cell, his wife said.
Eskinder is serving an 18-year sentence on vague terrorism charges, according to CPJ research. The U.N. Working Group on Arbitrary Detention condemned his 2012 trial and conviction and said it was connected to his “peaceful exercise of the right to freedom of expression.” The group found his arrest without warrant and prosecution was flawed, and the trial fell short of international standards of fairness.

Source: CPJ

Secret Brexit analysis warns of financial hit to Britain

Britain will be left worse off under all economic scenarios after Brexit, according to a leaked government analysis, with financial services, manufacturing and retailing among the industries worst hit. The document is expected to strengthen the hand of cabinet ministers pushing for a soft Brexit after March 2019, led by chancellor Philip Hammond, and the analysis was attacked by Brexiters.

The leak unleashed a blame game inside the government as to who was responsible for the analysis. Downing Street refused to disclose which Whitehall ministry had initiated the document, saying it was the product of a cross-departmental exercise. The paper, entitled EU Exit Analysis — Cross Whitehall Briefing and dated January 2018, looks at three of the most plausible Brexit scenarios. It was obtained by the online news and entertainment company Buzz Feed.

The analysis suggests a “no deal” scenario, under which Britain reverts to World Trade Organization rules, would reduce UK economic growth by 8 percentage points over the next 15 years compared with current forecasts. It says that under a free-trade agreement with the EU, growth would be 5 percentage points lower over the same period. The soft Brexit option of continued Norway-style access to the EU single market through membership of the European Economic Area — an arrangement ruled out by prime minister Theresa May — would lower growth by 2 percentage points. The analysis suggests Britain would suffer a larger hit to growth in the event of a so-called hard Brexit compared to a forecast produced by the Treasury before the 2016 referendum on EU membership. However, there would be a smaller hit in a soft Brexit. The Treasury’s 2016 document, dubbed Project Fear by the Leave campaign, said the WTO option was forecast to hit growth by 7.5 percentage points, compared to 6.2 percentage points with a free-trade agreement, and 3.8 percentage points with a Norway-style single market deal.

With the new analysis, a trade deal with the US is concluded in all the Brexit scenarios, offsetting some of the lost business with the EU when Britain leaves the single market and customs union. Mrs May is hoping to negotiate a deal with the EU that is somewhere between a traditional free-trade agreement and a Norway-style single-market deal, and there is no modelling for this outcome in the analysis. The paper acknowledges the risk to London’s status as a leading financial centre posed by Brexit. Every UK region would also be negatively affected in all the scenarios, with the north-east of England, the West Midlands and Northern Ireland facing the biggest impacts. Steve Baker, a minister at the Department for Exiting the EU, said the BuzzFeed article was a “selective interpretation of a preliminary analysis”, and “an attempt to undermine our exit from the European Union”. He added the government would release an “appropriate analysis” of the impact of Britain leaving the EU before MPs vote on the final Brexit deal. Mr Baker said he had not seen the leaked paper until Tuesday, adding: “It has not been led by my department.” However, government officials said work relating to the document began in August at the behest of a steering group chaired by a Dexeu civil servant. Dexeu denied this.

The Treasury denied that it was the “driving force” behind the paper. Recommended FT View: A vacuum in the UK cabinet puts Brexit transition at risk Janan Ganesh: Ditching May will fail to alter the course of Brexit Nick Clegg: Jacob Rees-Mogg is right, Britain risks vassal status Iain Duncan Smith, the former Conservative leader, told the BBC the analysis should be taken “with a pinch of salt” and that the timing of the leak was “highly suspicious”. Meanwhile Bank of England governor Mark Carney said he hoped for a rise in business investment next year once Brexit uncertainties were resolved. “My impression of UK businesses is that they are looking for greater certainty and there should be a pick-up in investment in 2019,” he added. Mr Carney said he understood there would be negative Brexit effects on the economy this year from uncertainties and from lower real incomes. “It is understandable our businesses are waiting to see what the future relationship [between the UK and the EU] is,” he added.

 

Source: Financial Times

UN says million displaced in Oromia-Somali conflict

A new report jointly released by the United Nations Office for the Coordination of Humanitarian Affairs (UNOCHA), the National Disaster Risk Management Commission (NDRMC) and International Organization for Migration (IOM) indicated that close to one million people have been displaced due to the conflict along the borders of the Oromia and Ethiopian Somali regional states.
According to the report released a week ago, nearly all districts along the borders of the two regions were affected by the displacement.
The report also stated that, preliminary data from the latest round of the International Office of Migration Displacement Tracking Matrix1 conducted in November, 2017 indicates that around one million persons have been displaced.

From this, nearly 700,000 are recorded in 2017 alone, still with a significant number registered after September 2017.
These displaced people are currently living in 400 locations across Oromia, Ethiopian Somali and Harari Regions, as well as Addis Ababa and Dire Dawa cities.
On the other hand, 637,000, almost 60 percent of the total displaced people are sheltered in camps. From this, the 68,000 are Ethiopian Somalis which are displaced between 2015 to end 0f 2017, according to the report.
The same assessment indicates that as of 16 January 2018, some 110,000 households are in need of urgent support. Out of this, more than 58,000 households are residing in Oromia Regional State while the 41,000 are from Ethiopian Somali.
At least 93,000 conflict-displaced school-aged children in Oromia and Ethiopian Somali Regions were forced to interrupt their education due to the displacement.
More than 1,500 children in Oromia and Ethiopian Somali regions are also reported to have been separated from their families.
Most of the assessed districts affected by the conflict in the two regions confirmed cases of sexual violence, psychosocial distress and domestic violence, reads the report.
It is to be recalled that, last month, the federal government has allocated half a billion birr to rehabilitate close to 500,000 displaced people in the two regions.
Particularly, the Oromia Regional State has already begun implementing its rehabilitation program for 86,000 people with a plan to settle them across 12 towns.
As far as assistant from the international community is concerned, the report reveals that to address gaps in assistance close to 29 million dollars is required from donor, in next month. Out of this, 15 million dollars is to provide water trucking to some 700,000 people.
Source:  The Reporter

Watch “ESAT Eneweyay January 29,2018” on YouTube

World’s doctor gives WHO a headache

Seven months into his tenure, the early moves of the WHO’s first African chief are stoking a backlash.
His supporters say Tedros Adhanom Ghebreyesus promised to shake the institution up. The critics, increasingly emboldened, say he’s undermining the World Health Organization’s effectiveness and putting its funding at risk.

The former Ethiopian health minister turned heads with his appointment of Zimbabwean dictator Robert Mugabe as a goodwill ambassador in October. Meanwhile, behind the scenes, Tedros — as he prefers to be called by Ethiopian tradition — was eschewing the normal hiring process for U.N. agencies, looking to increase gender and geographical diversity as quickly as possible. That’s unsettled some in the Geneva headquarters and the constellation of activists and researchers who work with WHO, who fear an overly political approach is bringing a culture change at the cost of credibility.
The latest disruptive move is his appointment of a little-known Russian official to run the WHO’s tuberculosis program, using a fast-track process, one month after meeting with President Vladimir Putin at a major gathering on the topic in Moscow.
The Mugabe appointment “was stupid, but this is a disaster,” said Mark Harrington, executive director of Treatment Action Group. Ahead of the appointment, TAG led an open letter from more than 40 civil society groups asking Tedros to use a transparent, competitive process to choose the next director of the Global TB Program, tasked with fighting the top infectious killer worldwide.
Reward for being retrograde
The December nomination of Tereza Kasaeva (an official at the Russian health ministry) prompted an editorial in the medical journal the Lancet, which described it as triggering a “potentially disabling controversy.”
“The domestic situation there is horrible. It’s probably one of the worst outside of Africa on TB infections” — Eduardo Gómez, King’s College London

“Russia has a poor record on TB and HIV,” write the editors of the journal, which is widely seen as the voice of the global health establishment. “Her appointment may be regarded as rewarding a country that does not deserve to be rewarded … WHO’s reputation — indeed, its political leverage — depends on the agency’s technical credibility.”
Russia is widely regarded as retrograde in its approach to treating the infectious disease, having developed a raging outbreak after the breakdown of the Soviet Union. Since 2000 or so, overall incidences are down and survival rates are up, but Russia is still a world leader on the proportion of infections that don’t respond to antibiotics; a recent study predicted one in three cases would be antibiotic resistant by 2040.
Kasaeva replaces Mario Raviglione, a leading TB expert with more than 25 years of experience fighting the bacterial infection.
Tedros says he’s just keeping a campaign promise to overhaul the agency in the wake of its high-profile failure to respond quickly to the 2014 Ebola crisis in West Africa. He is the first African to run the WHO — and the first director general chosen with a vote open to all member countries in May, overcoming what he called a “colonial mindset” among backers of his British rival.
Tedros’ advisers have defended his decision to name Mugabe a goodwill ambassador for noncommunicable diseases less than four months into the job as just a misguided effort to build bridges with a regional giant who, despite human rights violations and a long embrace of the tobacco industry, recently expressed openness to new commitments on health.
The offer was quickly retracted, but not before it triggered international condemnation. An opinion piece in the Washington Post even speculated that it was payback to Mugabe for securing the African Union’s support in the WHO election, or to China for its backing.

Tedros’ first appointments have already transformed the gender and geographic balance within the top ranks, even as they have raised concerns about a closed selection that downplays conventional expertise.
Of eight new directors chosen largely through a fast-track process, including Kasaeva, all but one are women.
Tedros is trying change the recruitment system to eliminate “unconscious biases that make it unfavorable for women to get the positions,” a top Tedros adviser, Senait Fisseha, said in an email. Until that can be accomplished, she said, he had made “limited appointments of diverse and highly qualified women” to move his vision forward.
That’s music to the ears of those who see an endless game of musical chairs that circulates people from one U.N. or international development agency to another. Often that means wealthy Western countries dictating to poorer countries how to deal with their problems in order to receive aid.
Vlad in Geneva
Diversity is a worthy goal, said Global Coalition of TB Activists CEO Blessina Kumar. But it shouldn’t come “at the cost of effectiveness and competency. You can’t trade one for the other,” she said.
“Merit was the first criteria for all appointments, while secondary consideration was given to gender and geographical diversity,” WHO spokesman Gregory Hartl said. “Dr. Tedros also sought to appoint qualified people with country-level experience, as a vital complement to the technical expertise that already exists within WHO. This will help to accelerate progress at the country level.”

Russian President Vladimir Putin met Tedros last year | Kirill Kudryavtsev/AFP via Getty Images
Kasaeva’s appointment has proved politically volatile both for Russia’s speckled track record in combatting TB, and because it’s seen as playing into Putin’s hands, helping the Russian president project power on the global health stage while he neglects patients back home.
“The domestic situation there is horrible. It’s probably one of the worst outside of Africa on TB infections,” said King’s College London’s Eduardo Gómez, the author of “Geopolitics in Health: Confronting Obesity, AIDS, and Tuberculosis in the Emerging BRICS Economies.”
In 2012, Russia rejected a $127 million grant from the Global Fund to Fight AIDS, Tuberculosis and Malaria, stifling many of the groups on the ground. On top of that, the federal government cut domestic TB funding in recent years, according to Gómez.
Nonetheless, in mid-November, Russia pledged $15 million toward fighting TB worldwide during a major U.N. TB conference in Moscow. The foreign aid is a typical Putin move, said Gomez. “This is an opportunity to reassert Russia’s dominance in global health.”
Putin addressed the gathering and met with Tedros. A month later, on December 15, Tedros announced Kasaeva’s appointment in an internal WHO email.
“I can’t see what the upside is other than political payback,” Harrington said.
Backlash on Tedros
Defenders say Russia’s TB program is improving — driven in part by Kasaeva — and that she may be the best hope for getting the country to change.
Vadim Testov, a former WHO official now working on Russia’s TB program, said he’s seen the government’s commitment increase over time, and that it’s “ready to provide” financing to make Russia’s domestic TB fight successful. He noted that new regulations from Kasaeva’s team have led to a sharper decrease in TB cases over the last five years.
Kasaeva “will have influence on Russian officials” in her WHO position, Testov predicted.
Many aren’t sold on Tedros’ new approach and fear that global health will suffer — especially if the WHO’s biggest donors get spooked.

The backlash shows the risks from Tedros’ effort to upend the status quo. Defenders say the same-old same-old at the U.N. hasn’t served patients on Ebola, TB or a range of other issues.
“Whatever we’ve been doing for the last quarter century isn’t working that well,” said Salmaan Keshavjee, a Harvard TB expert who has worked on the ground in Russia with Partners in Health.
He argued that WHO recommendations have in the past been ill-suited to Russia’s circumstances and that homegrown experts from emerging, populous economies may be in a better position to solve their own problems and bring a new perspective to the global effort.
“If you want to hold the BRICS countries’ feet to the fire, they have to be involved in health architecture,” Keshavjee said.
Budget strings
But many aren’t sold on Tedros’ new approach and fear that global health will suffer — especially if the WHO’s biggest donors get spooked.
Though ultimately blocked, U.S. President Donald Trump’s proposal to cut back on foreign aid — announced on May 23, the same day Tedros was elected to lead the WHO — has alarmed many in the organization. The recent controversies drive some worry that other large donors like the U.K. or Germany might be tempted to draw the purse strings tighter.

WHO Director General Ethiopia’s Tedros Adhanom Ghebreyesus delivers his speech after his election in Geneva in 2017 | Fabrice Coffrini/AFP via Getty Images
The U.S. contributes almost a quarter of the WHO’s $4 billion-plus annual budget.
Tedros’ doctorate is in community health, and he served as Ethiopia’s health minister for seven years — winning wide praise for strides in expanding contraception, fighting malaria and, yes, controlling TB.
But it may be his experience as Ethiopia’s top diplomat from 2012 to 2016 that seems most apposite now. During that period, he kept his country in the West’s good graces (and the aid money flowing) despite growing concerns about the regime’s human rights violations, by stressing Ethiopia’s position as a stable, strategic partner in the war on terror.
Tedros’ team includes plenty of conventional choices; Jane Ellison, a Brit, served as something of an olive branch to the WHO’s No. 2 state donor after the U.K. strongly backed its own candidate in a campaign that turned nasty. Tedros also named a German to a long-sought top post after Berlin stepped up donations and raised Tedros’ profile by inviting him to the G20 summit.
Source: Poletico